በሰሜን ሸዋ ዞን ሀገረ ማርያም ከሰም ወረዳ በወረዳዉ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ፕላን ኮሚሽን ቡድን አዘጋጅነት የተቋማት ሁለተኛ ሩብ ዓመት የስራ ክንዉን ከባለድርሻ አካላት ጋር ገምግሟል።
በወቅቱ የሰሜን ሸዋ ዞን መሬት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸዋንግዛዉ ሀይለሚካኤል፣የወረዳዉ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባይ ግዛዉ፣የወረዳዉ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መንገሻ ከበደ፣ጠቅላላ የወረዳዉ አመራሮች እና የተቋማት የማኔጅመንት አባላት ተሳትፈዋል።
አቶ አባይ ግዛዉ በመክፈቻ ንግግራቸዉ እንዳሉት የተቋማትን ዕቅድ ለማሳካት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በሁለተኛዉ ሩብ ዓመት የነበሩ ስኬቶችን በማስቀጠል እና የነበሩ ክፍተቶችን በመለየት በትጋት መስራት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
የወረዳዉ ተቋማት በሁለተኛ ሩብ ዓመት ያከናወኗቸዉን ተግባራት ሪፖርት በወረዳዉ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባይ የቀረበ ሲሆን አቶ ሸዋንግዛዉ፣አቶ አባይ እና አቶ መንገሻ የመድረኩ ተሳታፊዎችን አወያይተዋል።
ዝቅተኛ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ተቋማት ወደ ተሻለ አፈፃፀም መሸጋገር እንደሚገባቸዉ እና ዕቅድን መሰረት በማድረግ ሊሰሩ እንደሚገባ ተገልጿል።
የተቋማት ባለድርሻ አካላት ስራዎችን በጥራት እና በቅንጅት በመስራት የሚፈለገዉን ዓላማ ዳር ማድረስ እንደሚገባም ተጠቁሟል።
ያለዉን ወቅታዊ ሁኔታ በመቋቋም ከዚህም በላይ በቁጭት መስራት እንደሚጠበቅም ተገልጿል።
ተቋማት በቀጣይ የሚያከናዉኗቸዉን ተግባራት በሚፈለገዉ ልክ እንዲወጡ አቅጣጫ ተሰጥቷቸዋል።
የተቋማት ባለድርሻ አካላት በሁለተኛዉ ሩብ ዓመት ለተግባራቸዉ መሰናክል ለሆነባቸዉ እና ዝቅተኛ አፈፃፀም ላስመዘገቡበት ምክንያት ለመድረኩ ተሳታፊዎች አቅርበዋል።
ተሰብሳቢዎች በከፊል


