ተልዕኮ (Mission)
ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂን በወረዳው በማልማት፣ በማስፋፋት፣ በመጠቀምና የህብረተሰቡን ኑሮ በማሻሻል ለልማትና መልካም አስተዳደር መጐልበት የሚሰጠውን እገዛ በግንባር ቀደምትነት ማሳደግ፣
ራዕይ (Vision)
ሁሉም የሀገረ ማርያም ከሰም ወረዳ ሕዝብ ኑሮና ህይወት በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ የታገዘ ሆኖ ማየት፣
እሴቶችና የአሰራር መርሆዎች (Value and principles)
እሴቶችና የአሰራር መርሆዎች (Value and principles) የሂደቱን ዓላማ በማሳካትና የተጣለበትን ተግባርና ኃላፊነት በሚገባ ለመወጣት የሚከተሉትን እሴቶች በማጐልበት ይጠቀምባቸዋል፡፡
- ቀልጣፋና ውጤታማ አሰራርን እንዘረጋለን ፣
- ለደንበኞች እርካታ ቅድሚያ እንሰጣለን፣
- ምርጥ ተሞክሮን እናስፋፋለን፣
- ከኢኮቴ ዕድገት ጋር እንራመዳለን፣
- ግልጽነትን፣ ተጠያቂነትን፣ አሳታፊነትን እናረጋግጣለን፣
- ቡድናዊ የስራ መንፈስን እናሰፍናለን፣
- የሕዝብ አገልጋይነት ስሜትንና የስራ ተነሳሽነትን ባህል እናዳብራለን፣
የሂደቱ ተገልጋዮች
- የወረዳው መንግስት ሰራተኞች
- በወረዳው ውስጥ ያሉ ማህበረሰብ በሙሉ እና ሌሎችም
የምንሰጣቸው አገልግሎቶች
- የመሰረታዊ ኮምፒውተር ስልጠና መስጠት
- ሙያዊ እገዛ ማድረግ
- የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ጥገና
- የቪዶ ኮንፈርንስ አገልግሎት መስጠት
- ኢንተርኔት ማስጠቀም